YouTube



 https://youtube.com/channel/UC1uGQhXKz3wwjCgUNTpWR8g

አስተያየቶች

  1. ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን
    እኔ በሠው ነገር አልጠቁር አልከሳ
    የሠዉ መዉደድ ይስጥህ እንደ ቴዲ ካሣ።
    #እድለኛው_ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ!!!
    ቴዎድሮስ ካሳሁን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት እንደማተቡ የሰረጸው፣ኢትዮጵያን እልቡ ላይ የተነቀሳት፣የሀገር ፍቅርና መውደድ ሞልቶት ጢም ያለው፣በሙያ ቅቡልነቱም ሀገሩን ተሻግሮ አህጉር አቋርጦ በዓለም ላይ የናኜ ጠረፍ አጥ ድካ አልባ ሙያተኛ ነው፡፡
    ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን በሀገር ፍቅሩ በሙያ ክብሩ በሀገሬው ልብና ልቦና ዘልቆ ጠልቆ የገባ ጠቢብ ጥበበኛም ነው፡፡
    ምኑም የሚሰምርለት ሙዓዘ ዜማ ሣልሳዊው ቴዎድሮስ ሙዚቀኛ ብቻ ሣይሆን እሱ እራሱ ሙዚቃ ነው፣የደረበው የጥበብ ካባ የደፋው የተሰጥዖ አክሊልም ሞገስ አጎናጽፎታል፤ይህነቱን ለመመስከርም ሳር ቅጠሉ ድንጋይ አፈሩ ተፈጥሮ ሙሉ አንደበት አላቸው፡፡
    ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ልዑል የጥበብ ራስነቱ ብቻ አይደለም የሚስደንቀው፤ይለቁንም በወጀብ የማያናወጽ ብርቱ፤ግፊቱም የማያንገዳግደው ጽኑ መሆኑም እንጂ፡፡የሠብዕና ልዕልናውም ከከፍታው እንዳይወርድ አድርጎታል፤ይህም ለጥበብ አንቱነቱ በወል እንድንስማማ አድርጎናል፡፡
    ቴዎድሮስ ካሳሁን እሱ ስለፍቅር በፍቅር አቀንቅኗል፣ስለተፈትሮ ተቃኝቷል፣ታሪክን ከምሩ ዘክሯል፣በተልይም ስለሀገር አንድነት በአያሌው ሰብኳል፣ስለዕምነት በጥበብ አዚሟል በዚህም ምንቀረሹ ቴዎድሮስ ሙዚቃ ጥበብን አልዕሏታልም፤፤
    ልጁ ከጥበብ ጋር በክብር የተጋባ ጉድኝቱም የሠመረለት አክብሯት ያስከበራት ክብር የሚገባው ክቡር ሰው ነው፡፡

    ምላሽ ይስጡሰርዝ
  2. The boy Tewodros Kanyama
    : I don't care about human beings
    .
    # Lucky_Gonder_University !!!
    Tewodros Kassahun is an Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian
    Tewodros Kassahun is a wise man who has penetrated the hearts and minds of his country with his patriotism and professionalism.
    Not only is Tewodros III a musician, but he is also a musician.
    Not only is Teddy Afro a masterpiece of music, but he is also a man of unwavering power and resilience.
    Tewodros Kassahun has sung about love, explored nature, memorized history, preached national unity, and sang about faith in wisdom.
    His son, who was married to a wise man, was honored and respected.

    ምላሽ ይስጡሰርዝ

አስተያየት ይለጥፉ

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

አይሰው

እቴጌ ጣይቱ ብጡል (ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ)

ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ)