ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ ደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንጾር ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በጥቅምት 7 ቀን 1902ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት በቤተሰባቸው አጠገብና ባባታቸው አገር ደብረ- ኤልያስ ሄደው የግእዝ ትምሕርት ቤት ቅኔ ተቀኝተዋል። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ-ኤልያስ፣ በደብረ-ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ በ1918 ዓ.ም አዲስ አበባ በመሄድ በስዊድን ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ጊዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት ጣሊያን ወረራ ተከሰተ። የኢጣልያ ወረራ ሲከሰት ከልዑል ራስ ዕምሩ ኃይለሥላሴ ጦር ጋር በምዕራብ ኢትዮጵያ በአርበኝነት ሲዋጉ ቆይተው በመያዛቸው ጣሊያን ከልዑል ራስ ዕምሩ ጋር በግዞት ለሰባት ዓመታት በፖንዞ ደሴት ና በሊፓሪ ደሴት ታስረው ቆይተዋል። ከዚያም የተባባሪ ኃያላት ወታደሮች በ1935 ዓ.ም. ሲያስመልጧቸው በተመለሱበት ጊዜ በትምህርታቸው እንደገና በኦክስፎርድ ከገፉ በኋላ በተለያዩ የ መንግስት ተቋማት በተለይም በ ትምህርት ሚኒስቴር ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል። 1936 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኛ 1937 - 1938 - የኢትዮጵያ ቆንሱል በኢየሩሳሌም 1938 - በ International Telecommunications Conference አትላንቲክ ከተማ ፣ ኒው ጄርዚ ወኪል 1938- 1942 - በተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኒውዮርክ ሠራተኛ 1942- 1948 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይረክተርና ምክትል ...
ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን
ምላሽ ይስጡሰርዝእኔ በሠው ነገር አልጠቁር አልከሳ
የሠዉ መዉደድ ይስጥህ እንደ ቴዲ ካሣ።
#እድለኛው_ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ!!!
ቴዎድሮስ ካሳሁን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት እንደማተቡ የሰረጸው፣ኢትዮጵያን እልቡ ላይ የተነቀሳት፣የሀገር ፍቅርና መውደድ ሞልቶት ጢም ያለው፣በሙያ ቅቡልነቱም ሀገሩን ተሻግሮ አህጉር አቋርጦ በዓለም ላይ የናኜ ጠረፍ አጥ ድካ አልባ ሙያተኛ ነው፡፡
ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን በሀገር ፍቅሩ በሙያ ክብሩ በሀገሬው ልብና ልቦና ዘልቆ ጠልቆ የገባ ጠቢብ ጥበበኛም ነው፡፡
ምኑም የሚሰምርለት ሙዓዘ ዜማ ሣልሳዊው ቴዎድሮስ ሙዚቀኛ ብቻ ሣይሆን እሱ እራሱ ሙዚቃ ነው፣የደረበው የጥበብ ካባ የደፋው የተሰጥዖ አክሊልም ሞገስ አጎናጽፎታል፤ይህነቱን ለመመስከርም ሳር ቅጠሉ ድንጋይ አፈሩ ተፈጥሮ ሙሉ አንደበት አላቸው፡፡
ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ልዑል የጥበብ ራስነቱ ብቻ አይደለም የሚስደንቀው፤ይለቁንም በወጀብ የማያናወጽ ብርቱ፤ግፊቱም የማያንገዳግደው ጽኑ መሆኑም እንጂ፡፡የሠብዕና ልዕልናውም ከከፍታው እንዳይወርድ አድርጎታል፤ይህም ለጥበብ አንቱነቱ በወል እንድንስማማ አድርጎናል፡፡
ቴዎድሮስ ካሳሁን እሱ ስለፍቅር በፍቅር አቀንቅኗል፣ስለተፈትሮ ተቃኝቷል፣ታሪክን ከምሩ ዘክሯል፣በተልይም ስለሀገር አንድነት በአያሌው ሰብኳል፣ስለዕምነት በጥበብ አዚሟል በዚህም ምንቀረሹ ቴዎድሮስ ሙዚቃ ጥበብን አልዕሏታልም፤፤
ልጁ ከጥበብ ጋር በክብር የተጋባ ጉድኝቱም የሠመረለት አክብሯት ያስከበራት ክብር የሚገባው ክቡር ሰው ነው፡፡
The boy Tewodros Kanyama
ምላሽ ይስጡሰርዝ: I don't care about human beings
.
# Lucky_Gonder_University !!!
Tewodros Kassahun is an Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian, Ethiopian
Tewodros Kassahun is a wise man who has penetrated the hearts and minds of his country with his patriotism and professionalism.
Not only is Tewodros III a musician, but he is also a musician.
Not only is Teddy Afro a masterpiece of music, but he is also a man of unwavering power and resilience.
Tewodros Kassahun has sung about love, explored nature, memorized history, preached national unity, and sang about faith in wisdom.
His son, who was married to a wise man, was honored and respected.