ልጥፎች

ከፌብሩወሪ, 2021 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አማርኛ

  የአማርኛ ፊደላት (ሆሄያት) ፀጋዎች * በዚህ ዓለም ስለራስህ ከአንተ በላይ የሚያውቅ የለም! - ከድሮ አስተሳሰብ ጋር ተቸንክረው የቀሩ ቆሞ ቀሮች፦ 'ስለራስህ ሰዎች ይናገሩልህ እንጂ አንተ ዝም በል' አይነት ይትበሀል እያስፋፉ፤ አባባሉ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ተንሰራፍቷል። ሆኖም በአፍአዊ ደረጃ (ስለአንተ ሰው ይናገር) በሰፊው ቢናኝም፤ በተግባር ሲገለጥ በእያንዳንዱ ሰው ንግግር ውስጥ 'ከእኛ' ይልቅ 'እኔ' ጎልቶ መውጣቱ፤ ተቀባይነቱን ብላሽ/ ፉርሽ ያደርገዋል። በእርግጥም 'ሰዎች ስለአንተ ይናገሩልህ' የሚለው አገላለፅ ትህትናን ያዘለ ቢመስልም ስሁትና የሰዎችን ግለ _ ታሪክ የመቅበር አሉታዊ አቅሙ ከፍተኛ ነው። * ማነው ከአንተ ጋር ከልጅነትህ ጀምሮ አብሮ የተንከራተተ? * ማነው ከአንተ ጋር አቀበት ቧጥጦ ቁልቁለት ወርዶ የተፍገመገመ? * ማነው በውስጥህ ያመቅኸውን ዕንባና ሰቆቃ _ ብሶትና ምሬት የተጋራ? * ለምሳሌ፦ እንደ Misbah Kedir በወያኔ እስር ቤት አሳር ፍዳህን ስታይ፤ ማነው ከአንተ ጋር 'ቶርቸሩን' የቀመሰ? ማነው እንደ አንዷለም አራጌ በእስር ቤት ውስጥ አብሮህ ፊቱ የከሰለ? እኮ ማነው ስላንተ ከአንተ በላይ ምስክር? * ራስህን ካልወደድህ እመነኝ ቤተሰብህን ሀገርህንም ሆነ የሰውን ዘር አትወድም። (በራስ ወዳድነትና ራስን በመውደድ መሀከል ሰፊ ልዩነት አለ።) በእኔ ምልከታ ሰዎች ከበርካታ መልካም ሥራዎችህ መሀከል መጥፎውን መዞ የማጉላት ባህሪ ስለተጠናወታቸው ስላንተ እንዲናገሩልህ መጠበቅ፤ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ዐይን የሌለው ጥቁር ድመት የመፈለግ ያህል አዳጋች ይመስለኛል። በተቻለ አቅም ለህሊናህና ለፈጣሪህ ታማኝ ሁን እንጂ ስለአንተማ ተናገር! አንድ መሥሪያ ቤ

100 ways i love you

ምስል
100 ways to say “I love you” 100 ways to say “I love you” 1. You are beautiful. 2. I love your smile. 3. Here, let me get that for you. 4. I love seeing you wake up in the morning. 5. You are amazing. 6. I love (this) about you 7. Stay safe. Text me when you get there 8. I love when you do (this) 9. I think you’re beautiful when 10. You’re too good for me. 11. I don’t deserve you. 12. I care about you. 13. Don’t put yourself down like that. 14. I adore you. 15. I can’t stop thinking about you. 16. Seeing you makes me smile. 17. I need you by my side. 18. I’m thankful for you. 19. You make me a better person. 20. You complete me. 21. Have a good day at work 22. You’re the light of my life. 23. Seeing you makes my day. 24. I get butterflies every time we talk. 25. I’m so lucky to have you; I don’t know how I got so lucky. 26. You set my heart on fire. 27. I’ll walk you home. 28. I love to make you happy. 29. You’re my soulmate. 30. You’re my best friend. 31. I can’t wait to see you (agai

አይሰው

ምስል
🔑ራቁትክን ትወለዳለህ፤ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ 🔑 በጥርስ አልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ፤ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ። 🔐የሕይወትን ትግል እየዳህ ትጀምራለህ፤ አጎንብሰህ ትጨርሳለህ፡፡    🌍ዘመንም ተምኔታዊ ነው፡፡ 🌅መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሃል፤ ሠኞ ማክሠኞ ብለህ ተጉዘህ፤ እንደገና ሠኞ ትላለህ፡፡ እናም ሕይወት አዙሪት ናት! 🌽መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው፤የጀመርክበትን አትርሳ፤ መጨረሻህ ነውና፡፡የጀመርክበትን አትናቀው፤ ትጨርስበታለህና፡፡ ተራ ሠው ሆነህ ትጀምራለህ፤ ተምረህ ዕውቀት ብትጨምርም፤ ነግደህ ሃብት ብታገኝ፤ ተሹመህ በሕዝብ ላይ ብትሠለጥን፤ ክቡረ ክቡራን ሆነህ የወርቅ ካባ ብትለብስ፤ የምትጨርሠው እንደተራ ሠው አፈር ለብሠህ ነው

40 ስለ ምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች ዋና እውነታዎች ፡፡

40 ስለ ምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች ዋና እውነታዎች ፡፡ 1. ኢትዮጵያ 🇪🇹 ትልቁ የህዝብ ብዛት (114,963,588 ህዝብ ነው) ፡፡ 2. ሶማሊያ 🇸🇴 በቀጠናው ትልቁ የባህር ዳርቻ ነው ፡፡ 3. ኬንያ 🇰🇪 በክልሉ ከፍተኛው የሀገር ውስጥ ምርት ነው ፡፡ 4. ደቡብ ሱዳን region በቀጠናው ቀዳሚ የነዳጅ ዘይት አምራች ሀገር ነች ፡፡ 5. ጂቡቲ region በክልሉ ውስጥ እጅግ አነስተኛ የህዝብ ብዛት አላት ፡፡ 6. ታንዛኒያ 🇹🇿 በአፍሪካ ውስጥ ከፍተኛ ነጥብ አለው ኤምቲ ኪሊማንጃሮ ፡፡ 7. ኢትዮጵያ 🇪🇹 በአካባቢው ጠንካራ ወታደራዊ ኃይል አላት ፡፡ 8. ኢትዮጵያ 🇪🇹 በአፍሪካ ትልቁ ግድብ ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አላት ፡፡ 9. ኬንያ 🇰🇪 በዓለም ላይ ትልቁ የበረሃ ሐይቅ ፣ ቱርካና ሐይቅ አለች 10. ኡጋንዳ 🇺🇬 ለኬንያ ፣ ታንዛኒያ እና በአቅራቢያው ለሚገኙ የኮር.ሲ. 11. ሩዋንዳ 🇷🇼 ከአፍሪካ ንፁህ ከተማ አላት ፡፡ 12. ቡሩንዲ 🇧🇮 በአንድ ወቅት ንጉሦች ነበሯት ፡፡ 13. ኢትዮጵያ 🇪🇹 የንጉ king's ግንቦችና የአ Emperor ቤተመንግስቶች ታሪካዊ ስፍራዎች የበለፀጉ ናቸው ፡፡ 14. የኤርትራ የሴቶች ቁጥር በኤርትራ ውስጥ ከወንዶች በ 3 እጥፍ ይበልጣል ፡፡ 15. ኢትዮጵያ 🇪🇹 በምድር ላይ ትልቁ የአንበሳ ዝርያ አሏት ፣ በአንገቱ ላይ ጠቆር ያለ ፀጉር ያለው በርበሪ አንበሳ 16. ሱዳን 🇸🇩 ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ 🇪🇹 ከ 3500 ዓመታት በፊት የተጀመረ ረጅም ታሪክ አላቸው ፡፡ 17. ሱዳን 🇸🇩 በሰሜን ክልሏ ላይ የተወሰኑ ጥንታዊ ፒራሚዶች አሏት ፡፡ 18. 🇰🇪 🇺🇬 🇹🇿 በአፍሪካ ትልቁ የንፁህ ውሃ ሐይቅ የሆነው የቪክቶሪያ ሐይቅ አለው ፡፡ 19. 🇹🇿 እና

እቴጌ_ምንትዋብ በዙፋን ስሟ ብርሃን ሞገስ በ1698 ዓ.ም.

ምስል
እቴጌ_ምንትዋብ በዙፋን ስሟ ብርሃን ሞገስ በ1698 ዓ.ም. # እቴጌ_ምንትዋብ በዙፋን ስሟ ብርሃን ሞገስ በ1698 ዓ.ም. ከአባቷ ደጅአዝማች መንበር እና እናቷ ልዕልት እንኮይ በቋራ፣ ጎንደር ስትወለድ የክርስትና ስሟ ወለተ ጊዮርጊስ ነበር። እናቷ ልዕልት እንኮይ ከዓፄ ሚናስ ዘር የምትወለድ እንደነበረች ይጠቀሳል። ምንትዋብ በ18ኛው ክፍልዘመን ኢትዮጵያ ላይ ብዙ አሻራ ትታ የለፈች ንቁ፣ ሃይለኛና ተራማጅ መሪ ነበረች። ከባሏ ዓፄ በካፋ ዘመን ጀምሮ እስከ ልጇ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ እና ልጅ ልጇ ዓፄ እዮዋስ ዘመን ድረስ ለ40 አመታት የአገሪቱ እኩል መሪ የነበረች ናት። በዚህች መሪ ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ የህንጻዎች ግንባታና የቤተክርስቲያን ድረሰት፣ እንዲሁም ስነ ጥበብ እድገት ታይቷል። በፋሲል ግቢ የመጨረሻውን ግንብ ያስገነባችው ምንትዋብ ነበረች። ከልጆቿ የእድሜ አናሳነትና እራሷም በሰራቻቸው አንድ አንድ ስህተቶች ምክንያት በስልጣን በነበረችበት ዘመን የነበረው እድገትና ሰላም እርሷ ስታልፍ አብሮ አለፏል። እንግዴህ አገሪቱ ወደ ዘመነ መሳፍንት የተሻገረችው ልክ እርሷ እንዳለፈች ነበር። እቴጌ ምንትዋብ ከዐፄ በካፋ ጋር የተገናኘችው በተለየ ኣጋጣሚ ነበር። ዐፄ በካፋ በህዝብ ዘንድ ክብርን ካስገኘለት ስራው አንዱ ብዙ ጊዜውን በመሰዋት፣ እራሱን ደብቆ በግዛቱ ሁሉ እየተዘዋወረ ስህተት የተሰራውን ማቃናቱ ነበር። በዚህ ሁኔታ አንድ ቀን ተደብቆ ከጣና ሃይቅ በስተ ምዕራብ ሲጓዝ ቋራ ላይ ወባ ታመመና ከአንድ ገበሬ ቤት አረፈ። የስኮትላንዱ ተጓዥ ሐኪም ይጋቤ ሲተርክ “ወጣቷ ምንትዋብ ከመጠን በላይ ቆንጆ፣ ተግባቢና ልዝብ” የነበረች ሲሆን በካፋ ታሞ ያረፈበት ቤት ባለቤት ልጅ ነበረች። ምንትዋብ ታማሚ

እ_ጅ_ጋ_የ_ሁ_ሽ_ባ_በ_ው

ምስል
እ_ጅ_ጋ_የ_ሁ_ሽ_ባ_በ_ው www.ambachewmu3.blogspot.com    # እ_ጅ_ጋ_የ_ሁ_ሽ_ባ_በ_ው ስለ እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) አስተዳደግ ያካባቢዋ ልጅ ሆኜ መመልከት ባልችልም በ "ናፈቀኝ" ዘፈኗ የልጅነት ሕይወቷን መቃኘት አልቸገርም ።አንዷ አክስቷ አንድ ስም ሲያወጡላት ፣ሌላኛዋ በሌላ ሲጠሯት ፣አንድ ስም ሳይኖራት ማደጔን፣ቤታቸው ድግስ ሲደገስ ዘመዶቿ እነቄስ ሞገሴ ሲመጡ፣... ያለውን ስዕል በዚሁ "ናፈቀኝ" ዘፈኗ በቃላት ምናባዊ ጉዞ ምልከታዋን ታስዳስሰናለች፥ "ናፈቀኝ አያ ታዴ ሆዴ የሸበል አቧራ.. ....አይችልም ገላዬ የኔማ ታዴዋ.. .......ና ቁም ከኃላዬ እያለ ሲዘፍን ትዝታው ገደለኝ " በሀገሯ ከነበራት ሕይወት ወጥታ የአሜሪካን ኑሮን ስትጀምር እዛ ያለው ማህበረሰብ ግለኝነት የሰፈነበት፣ከጎረቤት ጋር መገናኘት የሚከብድበት ፣ብቸኝነት የሚያጠቃበት ፣ለራስ ብቻ መኖር የተመረጠበት መሆኑን ስትገልፅ ደግሞ ፦ "=====እያለ ሲዘፍን ትዝታው ገደለኝ ዛሬ በሰው ሀገር የሰው ከብት እያየሁ እያንገበገበኝ ------- ትላለች "የሰው ከብት "በምን ይገለፃል ቢሉ ለሆዱ ባደረ! እኔ እስከሚገባኝ ጂጂ የሰው ልጅ መገለጫው ያደገበት ማህበረሰብ ፍቅርና መተሳሰብ ነው ብላ የደመደመች ይመስላል ።ጂጂ በተለያዩ ዘፈኖቿ ስለ ሀገሯ፣ ስለህዝቧ ፣ስለ ማህበረሰቧ ያላትን ናፍቆት ና ጭንቀት ገልፃለች ። ጂጂ የሀገሯ ነገር ሁሌም ሕመሟ ነው ፣እንቅልፍ ይነሳታል ፤እህ----ህ--ህ ያሰኛታል ።ለዚህም ነው "እህ---ህ---"ብላ ስሜቷን የምታጋራን። ጎጃም ያረሰውን ለጎንደር ካልሸጠ ገንደር ያረሰውን ለኅጃም ካልሸጠ የሽዋ አባት ልጁን ለትግሬ ካልሰጠ የሐረር ነጋዴ

በራራ - ቀዳሚት አዲስ አበባ (1400 - 1887 ዓም)

በራራ - ቀዳሚት አዲስ አበባ (1400 - 1887 ዓም)

ምስል
በራራ - ቀዳሚት አዲስ አበባ (1400 - 1887 ዓም) በራራ - ቀዳሚት አዲስ አበባ (1400 - 1887 ዓም) እድገት ውድመት እና ዳግም ልደት፣ ያልተነገረው የኢትዮጵያ ታሪክ (በሀብታሙ መንግስቴ ተገኘ) በተለያዩ አጋጣሚዎች፣ በቃለ መጠይቅ፣ በጻፍኳቸው አጫጭር ጽሁፎች፣ ባሳተምኳቸው መጽሐፎች የኔ ትውልድ ከነበረው ቀናነትና የሃገር ፍቅር ባሻገር ከድንቁርና በመጣ ድፍረት የተናገራቸው፣ የጻፋቸውና የሰራቸው ስራዎች ዛሬ ሃገራችን ላለችበት አሳፋሪ ድህነት፣ ደም መፋሰስና አስከፊ የኑሮ ሁኔታ ጉልህ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል በማለት በተደጋጋሚ ተናግሬያለሁ። ይህ ትወልድ ተምሬያለሁ የምንለውን ትውልድ ብቻ የሚመለከት እንደሆነ ልብ በሉልኝ። ይህ በሀብታሙ መንግስቴ ተገኘ የተጻፈ መጽሐፍ የኔ ትውልድ ብቻ ሳይሆን ከኔ ትወልድ በፊት የነበረውንና ከኔ ትውልድ በኋላ የመጣው ትውልድ፣ በተለይ ታሪክን አስመልክቶ የነበረው እይታ ከድንቁርና በመጣ ድፍረት ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ግልጥልጥ አድርጎ በመረጃ የሚያሳይ ነው። ትልልቆቹ የሃገራችን ስመጥር የታሪክ ምሁራን ሳይቀሩ የኢትዮጵያን ታሪክ በተለይ የመካከለኛው ዘመን የሚባለውን ከ13ኛው ምዕተ ዓመት መጨረሻ ጀምሮ እስከ 16 ምዕተ ዓመት መጨረሻ የዘለቀውን ታሪክ አስመልክተው የሰነዱት ታሪክ ስህተት የተሞላበትና ትልቅ ጉድለት የታየበት እንደሆነ ያሳያል። በተለይ ደግሞ ወደ ዘመናችን ስንመጣ ታሪክን የፖለቲካ መሳሪያ ለማድረግ በማሰብ በጽንፈኛ ብሔርተኞች የተጻፉ መጽሐፎችና በምሁራኑ የሚቀርቡ ትርክቶች ከማናችንም በላይ በድንቁርና ላይ በተመሰረተ ድፍረት መጻፋቸው ብቻ ሳይሆን አደገኛነታቸውን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው። ይህ የዛሬው ጽሑፌ “በራራ”ን የተመለከተ የመጽሐፍ ግምገማ አይደለም። ይህን መጽሐፍ

አድዋ

ምስል
ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ ግብሩ እንቀላል ነበር ይሄን ጊዜ አበሻ፤ *** ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ መድፍ አገላባጭ ብቻለብቻ፤ *** የአድዋ ሥላሴን ጠላት አረከሰው ገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሰው፤ የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብር ማኅተም፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል ነው፡፡ የመላው ዓለም ተፈጥሮአዊ ግብር እና ሰብአዊ ክብር የታደሠው፤ በእውነትና በፍትህ ህልውናና ምልዓት ላይ የተሰካ ትልቅ ጥርስ የተነቀለው … በአድዋ የታላቅ ህዝቦች ታላቅ ድል ነው፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ስንሄድ 1066 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታላቁ ጦርነት የተደረገበትና ታላቁ ድል የተገኘበት ሥፍራ አድዋ ከተማና የከተማው ግድም ገመገሞች ይገኛሉ፡፡ በኢትዮጵያውያን አቡሻኽር (Julian calendar) የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም፤ ወይም በአውሮጳውያን የዘመን አቆጣጠር (Gregorian Calendar) February (የካቲት) መጨረሻ እና March (መጋቢት) መጀመሪያ ላይ 1896. ለጦርነቱ መነሻ የሆነው ውል የተፈፀመው በዚሁ ዘመን ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 468 ኪሎ ሜትር ርቀት ግድም ከውጫሌ ከተማ ግርጌ ከአምባሰል ተራራ ሥር ወሎ ውስጥ ንጉሥ ይስማ እየተባለ በሚጠራ ሥፍራ ነው፡፡ ሸልዶ ተራራ ወይም (ሶሎዳ ተራራ)፤ ማርያም ሸዊቶ፤ አዲ ተቡን፤ ረቢ አርእየኒ (እግዚሃር አሳየኝ)… በመሠኘት የሚታወቁት እነዚህ ገመገሞችና ተራራማ ሥፍራዎች ዋነኞቹ የጦር ግንባሮች ናቸው፡፡ በመቶ ሺህ የሚሠላ የኢትዮጵያ ገበሬ ሠራዊት ከአንድ ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የአውሮጳ ቅኝ ገዢ ወራሪዎችን ድባቅ ከመታና ረግጦ ካስወጣ በኋላ ከምሽቱ አራት ሰዓት ግድም (የካቲት 23 ቀን) እንዳማርያም ላይ ተሰባስቦ በአንድ እግሩ ቆሞ ቀኙን (ድሉን) ለሰጠው አምላክ ምሥ

ህይወት

ምስል
💚💛 ♥ የሕይወት አዙሪት! ሕይወት አዙሪት ናት፡፡ ረጅም ርቀት የተጓዝክ ቢመስልህም ነገር ግን የምትጨርሰው ከጀመርክበት ነው፡፡ ልብ በል! 🔑ራቁትክን ትወለዳለህ፤ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ 🔑 በጥርስ አልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ፤ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ። 🔐የሕይወትን ትግል እየዳህ ትጀምራለህ፤ አጎንብሰህ ትጨርሳለህ፡፡    🌍ዘመንም ተምኔታዊ ነው፡፡ 🌅መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሃል፤ ሠኞ ማክሠኞ ብለህ ተጉዘህ፤ እንደገና ሠኞ ትላለህ፡፡ እናም ሕይወት አዙሪት ናት! 🌽መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው፤የጀመርክበትን አትርሳ፤ መጨረሻህ ነውና፡፡የጀመርክበትን አትናቀው፤ ትጨርስበታለህና፡፡ ተራ ሠው ሆነህ ትጀምራለህ፤ ተምረህ ዕውቀት ብትጨምርም፤ ነግደህ ሃብት ብታገኝ፤ ተሹመህ በሕዝብ ላይ ብትሠለጥን፤ ክቡረ ክቡራን ሆነህ የወርቅ ካባ ብትለብስ፤ የምትጨርሠው እንደተራ ሠው አፈር ለብሠህ ነው፡፡ 🌸ልብ በል! ባለማወቅ ትጀምራለህ፤ በመዘንጋት ትጨርሳህ፡፡ ዕውቀት አላመጣህምና ዕውቀትም ይዘህ አትሄድም፡፡በለቅሶ ትጀምራለህ፤ በጭንቅ ትጨርሳለህ፡፡ በሠው እቅፍ ትጀምራለህ፤ በሠው ሸክም ትጨርሳለህ፡፡ ልደትህ ከሞትህ በምን ይለያል? ሞትህስ ከልደትህ በምን ይከፋል? ሕይወት መጀመሪያዋና መጨረሻዋ አንድ ነው፡፡ በዚህ የተነሣ ጠቢቡ እንዳለው ሁሉም የከንቱ ከንቱ ነው፡፡ ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም፡፡ ልብ በል! 🆔🔑የዓለም #ከንቱነት ግን ውበትዋ ነው፡፡ ዓለም አዲስ ነገር ቢኖራት እኛን እንዴት በፀፀተን፤ ሞት የእውነት መጨረሻ ቢሆን እንዴት በቆጨን!! ‹‹ርቀህ የሄድክ ቢመስልህም፤ ትልቅ ክብ ሰርተህ ተመልሰህ እዚህ ትመጣለህ፡፡ ዋናውን ተግባርክን ግን እስካሁን አልጀመርከውም፡፡››

#ህይወት

ያለምክንያት ከሄድክ በምክንያት አትምጣ" : ወዳጄ ህይወት ሰልፍ ውስጥ ሳለህ ልብ ልትላቸው የሚገቡ እነኚህን 19 ነጥቦች በአጽንኦት አንብባቸው! ፡ ➊."ያለፈ ነገር እንደማይቀየር አትርሳ!" : ላወቀበት ሰው ግን ያለፈው ለወደፊቱ የራሱ የሆነ ትምህርት አለው፤ ካለፈው ነገርህ ተማር እንጅ በፍፁም አታማርር፤ ማማረር ነገህን በጎ አያደርገውም። : ➋.የሰዎች ሃሳብ የአንተን ማንነት አይገልፅም! ማንነትህ አንተ ውስጥ ነው ያለው፤ መልካም አድርግ ሌላውን እርሳው የሁሉም ሰው የህይወት መንገድ (ጉዞ) ይለያያል፤ ለሁሉም ጊዜ አለውና ጊዜው በደረሰ ሰው ሁኔታ አትቅና። : ➌.መኪና ገዛ ብለህ "እኔስ" አትበል! : ጊዜህ ሲደርስ መኪናዎች ወይም ‘አውሮፕላን’ ትገዛለህ ፣ ያውም ለመኖር አስፈላጊ ከሆነ ፣ ደግሞስ እንዴት እንደገዛው የት ታውቃለህ? እርሱን ተወውና በራስህ ላይ አተኩር ፣ ያለህ ነገር በቂ ነው። : ➍."ለሰዎች ለደስታቸው እንጂ ለሀዘናቸው መንስዔ አትሁን!" : ►በሰዎች ደስታ→ደስ ይበልህ! : ►ለሰዎች→ክፉ አትመኝ፣ ፡ ►በሃዘናቸውም→አብረህ እዘን፣ ፡ ►ሰዎች ሲያዝኑ→አትደሰት፣ ፡ ►ሰው ከሆንክ→የሰው ነገር ይሰማህ፣ ፡ ይህ ማለት ግን ተንኮል እየሰሩ ከሚደሰቱ ሰዎች ጋር ተደሰት ማለት አይደለም። ሰው እያስከፋ ብሎም እየገደለ የሚደሰት አለ ፣ አንተ ከተጎዳው ሰው ጋ ሁን፣ አስተውል። : ➎."በጊዜ ስራ እንጂ ጊዜ ባንተ ላይ አይስራ!" ጊዜ የማይፈውሰውና የማይቀይረው ነገር የለም። አንተንም ጊዜው ይቀይርህ ዘንድ ፍቀድለት፤ በተሰጠህ ጊዜ ለመልካም ነገር ሱሰኛ ሁን። ➏. "መክሊትህን ፈልግ!" ውስጥህ የሚችለውና የሚያምንበት ተሰጥኦ ምን አለህ? ምን አይነት ስራ መስራት ትችላ

የኢትዮጵያ ጦር

የኢትዮጵያ ወታደሮች ሕይወት እንቆቅልሽ ጨዋታ ። የዚያድባሬ እብሪት ። ብኢኮ (ሜቴክ)ከሰራው እጅግ የመረረ በደል እነሆ ። """""""""""""""""""""""""""""""""""" twitter.com/ambachew123 እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ የታሪክ ባላንጋራ ከሆኑ እነሆ 45 ዓመታት ሆናቸው ። በመንግሥቱ ሀይለማሪያም ዘመነ መንግሥት ጣልያን እና እንግሊዝን የጀርባ አጥንት ( back bone of the war) በማድረግ ኢትዮጵያን በመውረር የግዛት አድማሷን በማስፋፋት ኦጋዴን እና አዋሽ መፋሰሻን እስከ ናዝሬት የመጠቅለል እቅድ ይዛ ተነሳች ። በቅጡ መንበሩን ያላስተካከለው የመንግሥቱ ሀይለማሪያም ወታደራዊ የሽግግር መንግሥት አስር ሺህ ወታደር የማይሞሉ ወታደሮች ወቅቱ ነበረው ። በአንፃሩ ሱማሊያ በድብቅ ለብዙ ዓመታት ያሰለጠነቻቸው እና በሚገባ የታጠቀ የነቃ የበቃ ድፍን ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ወታደሮች ወታደሮችን አሰልፋ ኢትዮጵያን ወረረች ። ኢትዮጵያን አንድም በድሮ ቂም በቀል ሁለትም በምንከተለው ርዕዮተ ዓለም የሶሻሊዝም አቀንቃኝነቱ ሦስትም የነበረንን የገናና እና የስትራቴጂ ቦታ ለመቀራመት ሶማሊያን በመጠቀም ወረራውን ድንገት የጦርነት ማብሰሪያ ጥይቷን ወደላይ በመተኮስ አስጀመረች። ደርግ በአንፃሩ በውስጥ የነበረውን የጠራ አቋም እና ተቃዋሚ ድርጅቶች መፍትሔ ያልሰጠበት ጊዜ በመሆኑ ጦርነቱ ለሶማሊያ ድል ያለ አጋጣሚ ነበር ። ሆኖም ግን አያሌ አርበኞች ገበሬዎች እና

ሞሶሎኒን በገዛ ሀገሩ ያርበደበደው ጀግና አብዲሳ አጋ (ከ1911-1970)

ሞሶሎኒን በገዛ ሀገሩ ያርበደበደው ጀግና አብዲሳ አጋ (ከ1911-1970) ጀግናው አብዲሳ አጋ በ1928 ዓ/ም የጣልያን ወረራ ወቅት ተማርኮ ወደ ጣልያን ከተወሰደ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀዳዶ በመቀጣጠል በመስኮት አምልጦ በርካታ ጀግንነቶችን የፈጸመ የኢትዮጵያ ወታደር ነው። ኮሎኔል አብዲሳ አጋ የተወለደው በ1911 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ፣ ወለጋ ዞን ነበር። በ12 ዓመቱ አባቱ በንዴት ወንድማቸውን በመግደላቸው ሲታሰሩ አብዲሳ አባቱን ለማስፈታት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ቢያደርግም ሳይሳካ በሞት ተቀጥተዋል። በኋላም በ14 ዓመቱ የኢትዮጵያን ጦር በመቀላቀል ሀገሩን ማገልገሉን ሀ ብሎ ጀመረ። አብዲሳ ጦሩን ከተቀላቀለ ከሁለት አመት በኋላ የአድዋን ሽንፈት ለመበቀል የዛተው ፋሺስት ሙሶሎኒ በድጋሚ ኢትዮጵያን ሲወር ሀገሩን ለመከላከል በ16 ዓመቱ ወራሪውን ጦር መዋጋት ጀመረ። ውጊያ ላይ ባጋጠመው የመቁሰል አደጋ ህክምና ላይ ከቆየ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ ፒያሳ አካባቢ በሚገኝ ቤት በቁም እስር ላይ ነበር። በኋላ ጣልያን ኢትዮጲያን እንዲያስተዳድር በሾመችው ግራዚያኒ ላይ የመግደል ሙከራ ከተደረገ በኋላ አብዲሳ አጋ እና ሌሎች 37 የሚሆኑ የቁም እስረኞች ተጠርጣሪ ተብለው በከባድ ስቃይ እስር ቤት ከቆዩ በኋላ በወቅቱ የጣልያን ግዛት በነበረችው በሶማሊያ በኩል ወደ ጣልያን ተወስዶ በሲሲሊ ደሴት በሚገኝ እስር ቤት እስረኛ ተደረገ። ከእስር ቤት ማምለጥ እና የአማጽያን ጦር ማደራጀት አልሸነፍ ባይነት መለያው የሆነው አብዲሳ ሁሊዮ ከተባለ ዩጎዝላቪያዊ የጦር እስረኛ ጋር በመተባበር ከባድ ጥበቃ ከሚደረግበት እስር ቤት ለማምለጥ ማሰላሰል ጀመረ። ተሳክቶለት ቢያመልጥ እንግዳ አገር እንደሚጠብቀው ቢያውቅም በነጻነቱ የማይደራደረው አብዲሳ የተሰጠውን የብርድ-ልብስ ቀዳዶ በመቀጣጠል በመ

ስነ-ልቦና

ከሚያጋጥመን የፀፀት ስሜት ለመውጣት የሚያግዙን ምክሮች። ----------------- . ጥፋትዎን አምነው ይቀበሉ - በእርግተኛነት በእርስዎ ምክንያት የተደረገውን መልካም ያልሆነ ነገር ጭንቅላትዎን ሙሉ በሙሉ አሳምነው ይቀበሉ። ጥፋቱ የርስዎ እንዳልሆነ አራስዎን ለመደለል አይሞክሩ። . ይቅርታ ይጠይቁ - አውቀውም ሆነ ሳያውቁ በእርስዎ ጥፋት ምክንያት የተጎዳ ሌላ ወገን ካለ በነገሩ እንዳዘኑ ገልፀው ከልብ ይቅርታ ይጠይቁ። . እራስዎን ከፀፀቱ ለማላቀቅ ይወስኑ - ጥፋትዎን አምነው ከተቀበሉ እና የበደሉትን ሰው ይቅርታ ከጠየቁ በሁዋላ፣ ከሚያሰቃይዎ የፀፀት ስሜት ነፃ መውጣት እንደሚገባዎት እራስዎን ማሳመን ይገባል። በዚህ ዓለም ላይ አውቆም ሆነ ሳያውቅ የማያጠፋ የለምና የእርስዎም ክስተት ከብዙዎቹ አንዱ እንደሆነ አምነው እራስዎን ነፃ ያውጡ። በነገሩ ውስጥ ከእርስዎ ቁጥጥር በላይ የሆነ ነገር ከነበረ፣ ይህንኑ ለራስዎ ተገንዝበው ወደሚቀጥለው የሕይወት ምእራፍ ለመሸጋገር ሳያመነቱ ይወስኑ። . ከክስተቱ ትምህርት ይወሰዱ - ያለፈው አልፏል እና በነገሩ እየቀዘሙ ከመሰቃየት፣ የበለጠ ለወደፊት ሕይወትዎ ጠቃሚ የሚሆነው ከክስጠቱ ትምህርት ወስዶ ተመሳሳይ ስህተት ውስጥ እንዳይገቡ መማር ነው። ልምድዎትንም ተጠቅመው ሌሎችን ለመርዳት እና ለመምከር ሊጠቀሙበት ይችላሉ። 5. በክስተቱ በማለፍዎ እራስዎን በ ከሚያጋጥመን የፀፀት ስሜት ለመውጣት የሚያግዙን ምክሮች። ----------------- 1. ጥፋትዎን አምነው ይቀበሉ - በእርግተኛነት በእርስዎ ምክንያት የተደረገውን መልካም ያልሆነ ነገር ጭንቅላትዎን ሙሉ በሙሉ አሳምነው ይቀበሉ። ጥፋቱ የርስዎ እንዳልሆነ አራስዎን ለመደለል አይሞክሩ። 2. ይቅርታ ይጠይቁ - አውቀውም ሆነ ሳያውቁ በእርስዎ ጥፋት ምክንያት የተጎዳ ሌላ ወገን

ወርቃማ አፈር

ወርቃማው ዐፈር ⚜ በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት በርካታ ተጓዦች ሃይማኖታቸውን ለማስፋፋት፣ ለጉብኝት እና ለስለላ ወደ ኢትዮጵያ ይመላለሱ ነበር፡፡ እነዚህ ተጓዦች ባብዛኛው ይመጡ የነበረው ከአውሮፓ አህጉር ሲሆን በመላው የኢትዮጵያ ምድርም ተዟዙረው ይጎበኙ ነበር፡፡ ከሰሜን ጫፍ ተነስተው እስከ ደቡብ ጫፍ ድረስ ከተጓዙ በኋላ እንደገና ደሞ ከምስራቅ ጫፍ ይጀምሩና እስከ ምዕራብ ጫፍ ድረስ ይጓዙ ነበር፡፡ በጉዞአቸውም የተራሮችን ጫፍ ይረግጡ ነበር፡፡ ወንዞችንም ይሻገሩ ነበር፡፡ በሸለቆዎች መሃል ለመሃልም ሰንጥቀው ያልፉ ነበር፡፡ በረሃዎችንም ያቋርጡ ነበር፡፡ እንዲህ እንዲህ እያሉ ጎብኝተው ሲያበቁ ያዩትን መልከዓ ምድሮች በሙሉ በካርታ አዘጋጅተው ለአጼ ቴዎድሮስ በስጦታ አስረከቡ፡፡ አጼ ቴዎድሮስም ካርታውን ከመረመሩ በኋላ “ካርታው እጅግ በጣም ጥሩ ነው፡፡ በዚህ ካርታ አማካኝነት የአባይን መነሻ ማወቅ እንችላለን፡፡ በዚህ ካርታ አማካኝነት የተራሮቻችንን ጫፍ ምን ያህል ከፍታ እዳለው መገንዘብ እንችላለን፡፡ የአገራችን ወንዞች የት የት እንደሚገኙ በቀላሉ መረዳት እንችላለን፡፡ ስለዚህ በሥራችሁ በጣም ተደስተናል፡፡ መልካም ሥራ ነው ያከናወናችሁት፡፡ ስለዚህ በጣም ተደስቼባችኋሉ፡፡” ብለው ለጎብኚዎች ትልቅ ግብዣ አደረጉላቸው፡፡ በግብዣው ወቅት እንጀራውና ወጡ፣ ጠላውና ጠጁ፣ ጮማው ሁሉ ሳይቀር የተትረፈረፈ ነበር፡፡ ግብዣው ካበቃ በኋላ ንጉሱ ለአውሮፓውያኑ የወርቅና የብር ስጦታም አበረከቱላቸው፡፡ ጎብኚዎችም በጣም ተደሰቱ፡፡ ይህ ከሆነ ከጥቂት ቀናት በኋላ ተጓዦቹ ወደ አገራቸው ለመመለስ ተነሱ፡፡ አጼ ቴዎድሮስም በርከት ያሉ አሽከሮቻቸውን ጠርተው “በሉ እነዚህን ተጓዦች መርከቡ ድረስ ሸኟቸው፡፡” ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡ፡፡ አሽከሮችም እሺ ብለው የተጓዦችን ሻንጣዎች ተሸክመ

አዳም ረታ

አዳም ረታ አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተመው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ”፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) [2] ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። ይህ የአጻጻፍ ስልቱ ሕጽናዊነት የሚባል ሲሆን ደራሲው በሌሎቹ መጻሕፍቱም ውስጥ በስፋት ተጠቅሞበታል፡፡ በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየ

አጤ ምኒልክና አርሲ

አጤ ምኒልክና አርሲ ✍ አጤ ምኒልክ እኛ ኢትዮጵያውያን ዛሬ በነጻነት እንኖር ዘንድ ብዙ መስዋዕትነትን ከፍለዋል ከዚህ ባሻገር በውጭ ሀገር የነበረውን ጥበባዊ ሥራ ወደ ኢትዮጵያ ያስገቡ ሰው ናቸው በመሆኑም ኢትዮጵያን መሥርተው በእግርዋ ያቆሙ የፍቅር ንጉሥ ናቸው ዳሩ ግን በዚህ ዘመን አጤ ምኒልክ በድለውናል ብለው ከሚያስቡ አካባቢዎች መካከል አንዱ  #አርሲ  ነው ነገር ግን እምዬ ምኒልክ ለአርሲዎች ያለቸውን ልዩ ፍቅር አንጋፋው የታሪክ ጸሐፊ  #ጳውሎስ_ኞኞ  👉"አጤ ምኒልክ" በሚለው መጽሐፋቸው ሲጽፉልን እንዲህ ብለዋል፦ "ደጃች ወልደ ገብርኤል አርሲን ለማቅናት ዘምተው አገሩን ቢይዙም የአርሲ ኦሮሞ አንገዛም እያለ በማስቸገሩ ምኒልክ በ1874 ዓ/ም ዘምተው ነበረ አብዛኛው የአርሲ ሕዝብ አሜን ብሎ ሲገብር አንዳንድ ባላባቶች አስቸግረው ነበር ምኒልክም በ1874 አርሲን መትተው አስገበርኩ ብለው ተመለሱ የምኒልክን መመለስ ያወቀው የአርሲ ሕዝብ እንደገና በገዢው በደጃዝማች ወልደገብርኤል ላይ አመፀ ምኒልክ በ1878 ዓ/ም እንደገና ወደ አርሲ ለመዝመት ግንቦት 5 ቀን ከእንጦጦ ተነሱ በሶዶ፣ በከንባታ፣ በዝዋይ አልፈው ጭላሎን፣ ሳቶን፣ ዲጋሎን አስገብረው አልባሶ ሜዳ ሠፈሩ በዚህም ጊዜ  #ኮጂ  የሚባለው የአርሲ ባላባት ለሊት ከደጃዝማች ወልደገብርኤል ሠፈር ገብቶ አደጋ አደረሰ 700 ያህል ሰዎችም ገደለ ምኒልክ የሠፈሩት ከደጃዝማች ወልደገብርኤል ሠፈር ራቅ ብለው ነበርና የአደጋውን መድረስ አልሰሙም በዚያም ለሊት አንዲት የሸሸች ሴት ከንጉሡ ሠፈር ገብታ የአደጋውን መድረስ ነገረች በማግስቱም ምኒልክ ለደጃዝማች ወልደገብርኤል ርዳታ ላኩ የእርዳታውን መድረስ ያላወቁ የአርሲ ሕዝብ እንደልማዱ ለሊት አደጋ ለመጣል ሲመጣ የምኒልክ ሠራዊት ፈጀው ከዚህ

ምርጥ__አባባሎችና ወርቃማ አባባሎች

ምርጥ__አባባሎች 1 አንዳንድ ሰዎች የሌሎችን ድክመት በመናገር * * * ራሳቸውን ጠንካራ ያስመስላሉ ! * * * 2 ሰው ጉብዝናህን በሹክሹክታ ድከመትህን በኡኡታ ያውራልና አትጨነቅ ! 3 አላስተዋይ ሰው ብትችል ዝም በል ያለዚያ ግን ያንተን ማንነት ከጀርባህ ሸሽገህ ስለ ሰው አታውራ ! 4 በስንዴው ማሳ ላይ እራሳቸውን ከፍ ከፍ ያደረጉ ሁሉ እንክርዳዶች ናቸውና ራስክን አቀርቅር ! 5 ምንም ቢሉህ ደካማ አስተሳሰብ ያለው ሰው እዘንለት እንጂ አትዘንበት ምክንያቱም የሚያስበው የሚያቀውን ያህል ነው ! እሱን በመጥላት የምታባክነው ጊዜ ራስህን ውደድበት !. ! 6 በራስ መተማመን ማለት ሌሎች ሲቀልዱብህ እና ሲያሾፉብህ በዝምታ ማለፍ ነው ! ለምን... ? ... ብትል ... አንተ ማን እንደሆንክ እና እነሱ ማን እንደሆኑ ጠንቅቀህ ስለምታውቅ ነው ፡፡ 7 ከአንተ ጀርባ ሆነው ስለሚያወሩ ሰዎች አትጨነቅ እነሱ የራሳቸውን የህይወት መንገድ መስመር ተስኗቸው ? የአንተን ስህተት በመፈለግ የተጠመዱ ናቸው ፡፡ ስለ እነሱ አትጨነቅ ምክንያቱም አንተ ሰዎች ምን ይሉኛል ብለህ የምትጨነቅ ከሆነ የሰዎች እስረኛ ነህ ! 8 ስራህ ከበረዶ 10ሺ የነጣ ቢሆንም ከሰው ትችት አታመልጥምና ለሰው ወሬ ጆሮ አትስጥ ! ! " አንተ እንደገባህ እንጅ ሰዎች እንደ ተረዱህ አትኑር ? ከአንተ በላይ ስለ አንተ የሚያውቅ ማንም የለምና ! 9 ሰው ከትልቅ ደግነት ይልቅ ትንሿን ስህተትህ የያል የሰው ፍፁም ስለሌለ አትጨነቅ ! ! ! ለህሊናህ ስትል ታመን መልካም አድርግ ጥሩ ስራ ? ከህሊናህ በላይአለቃ የለምና ! 10 ትክክለኛ_ሰው_ከሆኑ ፦ • • • ? ማንንም አይተቹ ትችት የሰዎችን ሞሯል ዝቅ ያደርጋል የበረታን ሰው ማበርታታት የነፍስ ኦክስጅን መስጠት ነው ! ሞሯል ሰውን ከፍ ና ጠንካራ የሚ

እቴጌ ጣይቱ ብጡል (ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ)

ምስል
እቴጌ ጣይቱ ብጡል (ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ) «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ » በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ 12 ቀን 1832 ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ 80 ቀናቸው ጥቅምት 27 ቀን 1833 ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። በልጅነት ዘመናቸው በዚሁ ደብር ውስጥ ዳዊትን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በጊዜው ይሰጡ የነበሩትን ሌሎች የሃይማኖት ትምህርቶች በየታላላቁ አድባራት በመዘዋወር ያጠናቀቁ ስለመሆናቸው ታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ። የተማሩባቸውም መፃሕፍት ተጽፈው ይገኙ የነበረበትን የ ግዕዝ ቋንቋ አጣርተው ያውቁ ነበር። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። እቴጌ ጣይቱ (ያኔ ወ/ሮ) ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በጥበብና በህይወት ፍልስፍና የላቀ ችሎታ ባለቤት መሆናቸው እየታወቀ መጣ:: ፀሐፊ ትዕዛዝ ገ/ሥላሴ እንደፃፉት ይህንን የጣይቱን ዝና ከሰሙ ልዑላን መካከል አንዱ በጐንደር ከአፄ ቴዎድሮስ ጋር ይኖሩ የነበሩት ወጣቱ ምኒልክ ተጠቃሽ ናቸው:: አቤቶ ምኒልክ ስለ እቴጌ ጣይቱ ዝና የሰሙት አብረው ይኖሩ ከነበሩት አሉላና ወሌ ብጡ

ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ)

ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ ደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንጾር ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በጥቅምት 7 ቀን 1902ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት በቤተሰባቸው አጠገብና ባባታቸው አገር ደብረ- ኤልያስ ሄደው የግእዝ ትምሕርት ቤት ቅኔ ተቀኝተዋል። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ-ኤልያስ፣ በደብረ-ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ በ1918 ዓ.ም አዲስ አበባ በመሄድ በስዊድን ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ጊዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት ጣሊያን ወረራ ተከሰተ። የኢጣልያ ወረራ ሲከሰት ከልዑል ራስ ዕምሩ ኃይለሥላሴ ጦር ጋር በምዕራብ ኢትዮጵያ በአርበኝነት ሲዋጉ ቆይተው በመያዛቸው ጣሊያን ከልዑል ራስ ዕምሩ ጋር በግዞት ለሰባት ዓመታት በፖንዞ ደሴት ና በሊፓሪ ደሴት ታስረው ቆይተዋል። ከዚያም የተባባሪ ኃያላት ወታደሮች በ1935 ዓ.ም. ሲያስመልጧቸው በተመለሱበት ጊዜ በትምህርታቸው እንደገና በኦክስፎርድ ከገፉ በኋላ በተለያዩ የ መንግስት ተቋማት በተለይም በ ትምህርት ሚኒስቴር ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል። 1936 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኛ 1937 - 1938 - የኢትዮጵያ ቆንሱል በኢየሩሳሌም 1938 - በ International Telecommunications Conference አትላንቲክ ከተማ ፣ ኒው ጄርዚ ወኪል 1938- 1942 - በተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኒውዮርክ ሠራተኛ 1942- 1948 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይረክተርና ምክትል

#ስውሩ #666

ስውሩ እጅ 666 (ኢሊሚናቲ) የአዲሱ የአለም መንግስት ታዋቂ የአለማችን ነገስታት:መንግስታትና ግለሰቦች የሚጠቀምባቸው አለም አቀፍ 666 (ኢሊሚናቲ) ምልክቶችና ትርጉማቸው እንዲሁም የአዲሱ የአለም መንግስት 666 (ኢሊሚናቲ) በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ:: ስውሩ እጅ 666 (ኢሊሚናቲ) የአዲሱ የአለም መንግስት ታዋቂ የአለማችን ነገስታት:መንግስታትና ግለሰቦች የሚጠቀምባቸው አለም አቀፍ 666 (ኢሊሚናቲ) ምልክቶችና ትርጉማቸው እንዲሁም የአዲሱ የአለም መንግስት 666 (ኢሊሚናቲ) በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ:: የአሜሪካን ገንዘብ አንድ ዶላር ሲሆን፣ ገንዘቡ ላይ ከቀኝ በኩል የሚታየው ከ1935 ዓ.ም ጀምሮ የተጨመረው ከአሜሪካ ሃገር ማህተም በስተጀርባ የነበረ ነው፡፡ ማህተሙ የጀርባ ቅርፅ እንዴት ሊኖረው እንደቻለ የቀረፁት ያውቁታል፡፡ አርማው የአዲስ የአለም መንግስት ስርአትና የኢሉሚናቲ የሀረም/ፒራሚድ ማህተም የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ማህተም የሰይጣናዊው የሴራው እቅድ የንድፋዊ መግለጫ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ከላይ “Annuit Coeptis—ጅማሪያችንን መርቆታል” ሲል ከስር ደግሞ፣ “Novus Ordo Seclorum—የዘመናቱ አዲስ ጅማሮ” ይላል፡፡ ከሀረሙ ጫፍ ያለችው ዓይን የሆሩስ–የፀሃይ አምላክ ሁሉን ተመልካች ዓይን የሚሉት ሲሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ብርሃን መልአክ /ሉሲፈር/ን ያመለክታል፡፡ በባእድ አምልኮ ዶክትሪን መሰረት እንደሚታመነው በመንፈስ እና ቁስ አካል ውህደት (ሀረሙ ከድንጋይ፣ አለትና አፈር የተሰራው የማያውቀውን (unconscious) አካል ሲወክል ከላይ የምታበራው ዓይን ያለባት ደግሞ ቁሳዊ ባልሆነ አካል –ብርሃን ወይም መንፈስ– የሚወክል ሲሆን አዋቂው (conscious) አካል ነው፡፡ ከስር ጀምሮ ወደ ላይ የደረሰም አዲስ ሁኖ ይፈጠራል፡፡ ሀረሙ የሚያመላክተው ከ