ልጥፎች

ያለፈ ነገር እንደማይቀየር አትርሳ!"

ምስል
➊."ያለፈ ነገር እንደማይቀየር አትርሳ!" : ላወቀበት ሰው ግን ያለፈው ለወደፊቱ የራሱ የሆነ ትምህርት አለው፤ ካለፈው ነገርህ ተማር እንጅ በፍፁም አታማርር፤ ማማረር ነገህን በጎ አያደርገውም። : ➋.የሰዎች ሃሳብ የአንተን ማንነት አይገልፅም! ማንነትህ አንተ ውስጥ ነው ያለው፤ መልካም አድርግ ሌላውን እርሳው የሁሉም ሰው የህይወት መንገድ (ጉዞ) ይለያያል፤ ለሁሉም ጊዜ አለውና ጊዜው በደረሰ ሰው ሁኔታ አትቅና። : ➌.መኪና ገዛ ብለህ "እኔስ" አትበል! : ጊዜህ ሲደርስ መኪናዎች ወይም ‘አውሮፕላን’ ትገዛለህ ፣ ያውም ለመኖር አስፈላጊ ከሆነ ፣ ደግሞስ እንዴት እንደገዛው የት ታውቃለህ? እርሱን ተወውና በራስህ ላይ አተኩር ፣ ያለህ ነገር በቂ ነው። : ➍."ለሰዎች ለደስታቸው እንጂ ለሀዘናቸው መንስዔ አትሁን!" : ►በሰዎች ደስታ→ደስ ይበልህ! : ►ለሰዎች→ክፉ አትመኝ፣ ፡ ►በሃዘናቸውም→አብረህ እዘን፣ ፡ ►ሰዎች ሲያዝኑ→አትደሰት፣ ፡ ►ሰው ከሆንክ→የሰው ነገር ይሰማህ፣ ፡ ይህ ማለት ግን ተንኮል እየሰሩ ከሚደሰቱ ሰዎች ጋር ተደሰት ማለት አይደለም። ሰው እያስከፋ ብሎም እየገደለ የሚደሰት አለ ፣ አንተ ከተጎዳው ሰው ጋ ሁን፣ አስተውል። : ➎."በጊዜ ስራ እንጂ ጊዜ ባንተ ላይ አይስራ!" ጊዜ የማይፈውሰውና የማይቀይረው ነገር የለም። አንተንም ጊዜው ይቀይርህ ዘንድ ፍቀድለት፤ በተሰጠህ ጊዜ ለመልካም ነገር ሱሰኛ ሁን። ➏. "መክሊትህን ፈልግ!" ውስጥህ የሚችለውና የሚያምንበት ተሰጥኦ ምን አለህ? ምን አይነት ስራ መስራት ትችላለህ? አስተውል ጓደኛህን አትመልከት ፣ ትለያያላችሁና። አለማችን በትምህርት ብቻ ወይም በጥበባት ብቻ ወይም በተወሰኑ ዘርፎች አይደለም እየኖረች ያለችው። በጣ

እጅግ በጣም የሳትነው ብዙ ነገር አለ።

ምስል
እጅግ በጣም የሳትነው ብዙ ነገር አለ። እነዛ የሶሻሊዝምን ጽንሰ-ሃሳብ በውል ያልተረዱ፣ ጺማቸውንና ጠጉራቸውን የሚያሳድጉ የ60'ዎቹ ተማሪዎች "ማርክስ እንዳለው …፣ ኤንግልስ እንዳለው…፣ ሌኒን እንዳለው …፣ ማኦ እንዳለው …፣ ቼጉቬራ እንዳለው…፣ ሆቺሚኒ እንዳለው…፣ እስታሊን    እንዳለው…፣ " ወዘተ እያሉ ታሪካችና እሴቶቻችን እንዲጠለሽ አድርገዋል። Twitter  የ60'ዎቹ ትውልድ ባህሉን፣ ወጉን፣ ሥርዓቱን፣ ሥነ-ጽሑፉን፣ ታሪኩን ጭምር ነቅፎ በባዶ እጁ ነው የሸፈተው። ከቆዳ ቀለማቸው በስተቀር የኢትዮጵያዊነትን ነባር እሴት፣ ባህል፣ ወግ፣ ታሪክ... ፍቀው የነማርክስንና የነስታሊን ፍልስፍና ይዘው ነው የሸፈቱት። መፍትሔው እግዚአብሔርን መካድ የመሰለው ማርክሲዝምን ርዕዮተ ዓለም አድርጎ የተነሣው የሶሻሊስት አቀንቃኝና የብሔር ፖለቲካን ቀይጦ የያዘው ወጣት የኢትዮጵያዊነት አስኳል ከውስጣቸው አውጥተው ጣሉት። በአጉል ማርክሳዊ-ሌኒናዊነት እግዚአብሔር-አልባ አደረጋቸው። ትውልዱንም ሳይቀራረብ የሚተያይ፣ በማያውቀው ታሪክ ተተብትቦ ወደኋላ እንጂ ወደፊት መራመድ የማይችል፣ ባዕድን እንደ ዘመድ፤ ዘመድን እንደ ባዕድ የሚመለከት ሽባ ትውልድ አደረጉት። እንጥፍጣፊ ሳያስቀር የኩራቱንና የክብሩን ካባ አውልቆ ጣለው፣ ኢትዮጵያዊነትን በአፍጢሙ ደፋው፣ የመንፈስ ኃይሉ ደቀቀ፣ በመጨረሻም አንገቱን ደፋ፣ ችግሩንም ሁሉ ለመፍታት የፈረንጆችን እርዳታ የሚፈልግ ትውልድ ተፈጠረ። ቀጥሎስ.....ቀጥሎ ደግሞ የኢትዮጵያ እደ ጥበብ ሠራተኞችን፦ ለምሳሌ ብረት ሰሪዎችን "ቀጥቃጭ"፣ ልብስ ሰሪዎችን "ሸማኔ"፣ ቆዳ ሰሪዎችን "ፋቂ" በማለት እንዲጠፉና ከማኅበረሰቡ እንዲገለሉ አደረገ። ይህ ቅስቀሳ በሚሲዮናውያን የተ

የታንጉት ምስጢር

ምዕራፍ አንድ ከፋሲል ዘመነ መንግሥት ጀርሞ የሥልጣን ማዕከል ሆና የኖረችው የጎንደር ከተማ ማኅበራዊ እንቅስቃሴ፤ ከአዲሱ የቴዎድሮስ ሥርዓት፤ አዲስ የጦር አበጋዞች አዲስ ሠራዊት ጋር ለመስማማት አዲስ ቅኝት ሲከረክር ድንገተኛ ከባድ እንግዳ ወይም ሠርገኛ ደሶበት የቤቱን ዕቃ የሚያተረማምሰ ባለቤት መስሏል። የሚተራመሰው ማኅበራዊ ግንኙነት ግን በወጉ ሊቀመጥ አልቻለም። ሊቀመጥም አይችልም ነበር። ጎንደር ጥንት ከተቆረቆረች፤ ፈጽሞ የተለየ አዲስ ማኅበራዊ ዛፍና ፍሬ ለምቶባት ነበር። ከተማ እንደ ማሳ ነው። ማኅበራዊ አኗኗር ማኅበራዊ አስተሳሰብ የዘራዉን ማኅበራዊ ሕይወት ያበቅላል፤ ያሸታል፤ ያፈራል፤ ማሳው በወቅቱ ካልታረመ ዝባዝንኬው እስከ ገሰሱ በርክቶ ይገኛል። ማሳው ራሱ በሚገባ ካልተያዘ እንክርዳዱም፤ እረሙም እየበዛ ሔዶ ጠቃሚ ፍሬ የማይሰጥበት ጊዜ ይመጣል። ዕዳሪ ይሆናል። የጎንደር ከተማ ማኅበራዊ ሕይወትም አንድ መቶ ስልሳ ዓመት በሚሆን ጊዜ ውስጥ እየተበላሸና ከመልካም ፍሬ ይልቅ፤ ሙጃ የበዛበት ማሳ እየሆነ ሔዶ ነበር። ፋሲል፤ ጎንደርን ሲቆረቁር ሠራዊቱ ገና መዝናናት ያልለመደ ለተግባሩ ያልተሰላቸ፤ ምቾት ገና ያላሰናነፈው፤ ትዕዛዝ አቆብቁቦ የሚጠባበቅ ትኩስ አፍለኛ ነበር። አላማም ነበረው። በሃይማኖት ምክንያት ተነሥቶ የነበረው ሁከትና የርስ በርስ ጦርነት ጨርሶ እስኪረጋጋ ከሥፍራ ሥፍራ እየተንቀሳቀሰ አጥፊ ይቀጣል። አስቸጋሪ ይነገራል። ሰላም ያስከብራል። ከጦር መሪዎቹ ሌላ በስብከት፤ በውግዘት፤ በምርቃት መንፈሳዊ ሕይወቱን የሚያንቀሳቅሱና የሚመሩ፤ ከዚያም አልፎ መስቀል ከሰላጢን ይዘው አብረውት የሚሰለፉ፤ አዲሱን የካቶሊክ ሃይማኖት ነበሩ። የነጋሹም፤ የአንጋሹም፤ የዘማቹም የቀዳሹም ማኅበራዊ ሕይወትና አስተሳሰብ በአንዳች ዐይነት የዘመቻና የዘማች መንፈስ የ

ዕንቁጣጣሽ_እና_የከንፈር ወዳጅ

ምስል
#ዕንቁጣጣሽ_እና_የከንፈር ወዳጅ የኢትዮጵያ ሕዝብ በየዓመቱ በታላቅ ስሜት ከሚያከብራቸውና ከሚያዘክራቸው በዓላት አንዱና ተወዳጅ የዘመን መለወጫ በዓል ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በየዓመቱ በታላቅ ስሜት ከሚያከብራቸውና ከሚያዘክራቸው በዓላት አንዱና ተወዳጅ የዘመን መለወጫ በዓል ነው። እንደ ዕፅዋት ሁሉ ሰው በመስከረም ላይ በተስፋ ስሜት ይለመልማል። ከቅዱስ ዮሐንስ ዋዜማ ጀምሮ በየቤቱ ጨፌና ቄጠማ ይጐዘጐዛል። አበባ በሥርዓት እየተዘጋጀ በየቦታውይቀመጣል። በተለይም ልጆች አዳዲስ ልብሳቸውን ለብሰው በደስታ ይፈነድቃሉ። በአመሻሽ ላይ ችቦ አቀጣጥለው «እዮሐ አበባዬ መስከረም ጠባዬ፣ እዮሐ የበርበሬ ውኃ፣ በሸዋ በጐንደር በትግራይ በሐረር... ያላችሁ እንዴት ከረማችሁ፣እንኳን ከዘመን ዘመን አሸጋገራችሁ። እንጉርጉሮገባሽ በየአመቱ ያምጣሽ..» እያሉ ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች (በተለይ በገጠር) ሲዘፍኑና ሲጨፍሩ ያድራሉ። የሚያበሩት ችቦና የሚያነዱት እሳት በግርማ ምሽት ሲንቀለቀል ውጋገኑ ካገር አገር ከሰፈር ሰፈር ከቦታ ቦታ ይታያል።በዕንቁጣጣሽ መዓልት በተደመረው አድባር ሰፈርተኞች ከርቀትም ከቅርበትም ይሰበሰባሉ። አባቶች ይመርቃሉ። «ዝናሙን ዝናመ ምሕረት፣ እህሉን እህለ በረከት ያድርግልን፣ ሰላም ይስጠን፣ እህል ይታፈስ፣ ገበሬ ይረስ፣ አራሽ ገበሬውን፣ ሳቢ በሬውን ይባርክ፣ ቁንጫን፣ አንበጣን፣ ትልን... ያጥፋ፣ ምቀኛን ሸረኛን ያጥፋ፣ ወጡ ገቡ ሰቡ ረቡ የሚለውን ሁሉ እግሩን ቄጠማ ዓይኑን ጨለማ ያድርገው፣ ያርገው፣ ያረገው፣...» ይባባላሉ። እናት አባት ዘመድ አዝማድ በልጆቻቸውና በወዳጅ ዘመዶቻቸው የተበረከተላቸውን የዕንግጫ ጉንጉን (የአበባ አክሊል) በራሳቸው፣ እንጀራ ማቡኪያቸው፣ በመሶባቸው፣ በወጋግራቸው... ላይ ያስራሉ። ይህም የአበባ ጉንጉን ተፈትቶና ወጥቶ የ

#TPLFISATERRORISTGROUP

ምስል
Cities are being cleared of TPLF forces. Strategic areas have been taken over by the Defense Forces. The 5 week TPLF Aura jump is coming to an end. The central city of Gashena is liberated. The city of Delantawa is also under Ethiopian control. Recently, their master helped her, slaughtered a lamb, and ate a roast beef, which relieved heranxiety. #TPLFISATERRORISTGROUP 🍃 click  By the way, their master and some TPLF warlords escaped for a while. There was a black cloud over the ground, but there was an opportunity for the Air Force to set fire to their convoys. #TPLFISATERRORISTGROUP  🍃 click  Areas affected by the TPLF's brutality and looting, such as Arbit, Steish, are breathing a sigh of relief today. Ethiopian forces continue to write history and clean up the TPLF. Lalibela is seen in the distance. Mersa, Urgesa are already free. #TPLFISATERRORISTGROUP  🍃 click  The TPLF, which has been holding a section in Woldia, is looking for Mary's way. In cutouts, the gel is

ወያኔ_የቤተ_ሣጥናኤል (Church of Satan)አምላኪዎች ናቸው

# ወያኔ_የቤተ_ሣጥናኤል (Church of Satan)አምላኪዎች ናቸው  The end justifies the means.› በድምሩ ከአምስት ሚሊዮን ሕዝብ የወጡ ‹ጥቂት›የትግሬ ገዢዎች የ110 ሚሊዮን ሕዝብ ዕጣ ፋንታ ይወስናሉብሎ በሰው ልጅ አእምሮ ማሰብ የሚቻል አይደለም ነበር ፡፡ ነገርግን ይሁን ያለው ከመሆን አይዘልምና እየተገረሙ የዓለምን አካሄድ በትዝብት ከመቃኘት በስተቀር ምንም ማድረግ አይቻለንም፡፡ በብሂልህ “ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራልትል የለም? ወደህ ተሰደድህ ? ወደህ ትራባለህ? ወደህ ሀገር አልባ ትሆናለህ? አብዛኞቹ የዓለም ቢሌነሮች እነማን ናቸው? የዓለምን ትልቅ ሥልጣን በእጅ አዙርና በቀጥታ የተቆጣጠሩት እነማን ናቸው? ወዴት እየነዱህ ነው? ወደ ጥፋ ወይንስ ወደ ልዕልና? በኢትዮጵያስ ያንን ዓለም አቀፍ ነፀብራቅ ቁልጭ ብሎ እያየኸው አይደለምን? ዘመኑ የጥቂቶች ነው ወዳጄ ልቤ፡፡ ሁሉን ቢያወሩት ሆድ ባዶይቀራል፡፡እንደውነቱ ውሸት የሚናገር ሰው በሥቃይ ውስጥ ያለ ነው፡፡ እውነትን የሚናገር ሰው ግን በሥቃይ ውስጥ ላለመኖር የቆረጠ ሰው ነው፡፡ እውነትን በመናገር ብዙ ነገር እናጣለን፡፡ከቅርብ ጓደኛና ዘመድ ጀምሮ የምናጣው ብዙ ነገር ነው – በዓለማዊ አስተሳሰ መብል፣መጠጥ፣ ድሎት፣ሥልጣን፣ፍቅረኛንና የትዳር አጣማሪን ሳይቀር ብዙ ነገሮችን ልናጣ እንችላለን፡፡ ሀሰት መታወቂያዋ በሆነ ዓለም ውስጥ ስንኖር እውነትን ለመናገር ከቆረጥን እንደዕብድ ልንቆጠርና በውግዘት ከአካባቢናዐከማኅበረሰብም ጭምር ልንገለል እንችላለን – ያኔ ሃይማኖት፣ባህል ወግና ልማድ የተባለው ይበልጡን በውሸት የተቃኘው ማኅበራዊ ሥርዓት ሁሉ ይከዳህና ከሕገ ወጦቹ ጋር ሲወግንብህ መግቢያ ቀዳዳ ታጣለህ – ደግሞም ያኔ የምትኖርባት ዓለም የሀሰት እንጂ የእውነት መገለጫዐእንዳልሆነች

ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን

ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን እኔ በሠው ነገር አልጠቁር አልከሳ የሠዉ መዉደድ ይስጥህ እንደ ቴዲ ካሣ። #እድለኛው_ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ!!! ቴዎድሮስ ካሳሁን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት እንደማተቡ የሰረጸው፣ኢትዮጵያን እልቡ ላይ የተነቀሳት፣የሀገር ፍቅርና መውደድ ሞልቶት ጢም ያለው፣በሙያ ቅቡልነቱም ሀገሩን ተሻግሮ አህጉር አቋርጦ በዓለም ላይ የናኜ ጠረፍ አጥ ድካ አልባ ሙያተኛ ነው፡፡ ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን በሀገር ፍቅሩ በሙያ ክብሩ በሀገሬው ልብና ልቦና ዘልቆ ጠልቆ የገባ ጠቢብ ጥበበኛም ነው፡፡ ምኑም የሚሰምርለት ሙዓዘ ዜማ ሣልሳዊው ቴዎድሮስ ሙዚቀኛ ብቻ ሣይሆን እሱ እራሱ ሙዚቃ ነው፣የደረበው የጥበብ ካባ የደፋው የተሰጥዖ አክሊልም ሞገስ አጎናጽፎታል፤ይህነቱን ለመመስከርም ሳር ቅጠሉ ድንጋይ አፈሩ ተፈጥሮ ሙሉ አንደበት አላቸው፡፡ ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ልዑል የጥበብ ራስነቱ ብቻ አይደለም የሚስደንቀው፤ይለቁንም በወጀብ የማያናወጽ ብርቱ፤ግፊቱም የማያንገዳግደው ጽኑ መሆኑም እንጂ፡፡የሠብዕና ልዕልናውም ከከፍታው እንዳይወርድ አድርጎታል፤ይህም ለጥበብ አንቱነቱ በወል እንድንስማማ አድርጎናል፡፡ ቴዎድሮስ ካሳሁን እሱ ስለፍቅር በፍቅር አቀንቅኗል፣ስለተፈትሮ ተቃኝቷል፣ታሪክን ከምሩ ዘክሯል፣በተልይም ስለሀገር አንድነት በአያሌው ሰብኳል፣ስለዕምነት በጥበብ አዚሟል በዚህም ምንቀረሹ ቴዎድሮስ ሙዚቃ ጥበብን አልዕሏታልም፤፤ ልጁ ከጥበብ ጋር በክብር የተጋባ ጉድኝቱም የሠመረለት አክብሯት ያስከበራት ክብር የሚገባው ክቡር ሰው ነው፡፡ ይህንን ሰው ያከበረ እንደምን አይከበር፤እናም ለእኔ ጎንድር ዩኒቨርሲቲ ዕድለኛ ነው ከብዙ ሳይንስ ተመራምረው ማህበረሰብን አጥንተው ዶክትሬት ካገኙ ግን ቡዙ ህይወታቸውን ጥላቻ እና ቂምን ከሚዘሩ የፍቅር ጠላቶች ይልቅ የቴዲ የክብር ዶክትሬት እጅግ ዋጋ