Chemical Formula አገናኝ አግኝ ፌስቡክ ቲዊተር Pinterest ኢሜይል ሌሎች መተግበሪያዎች - ዲሴምበር 20, 2020 file:///storage/emulated/0/Chemical formula.pdfhttps://www.ambachewmu3.blogspot.com አገናኝ አግኝ ፌስቡክ ቲዊተር Pinterest ኢሜይል ሌሎች መተግበሪያዎች አስተያየቶች
አይሰው - ፌብሩዋሪ 23, 2021 🔑ራቁትክን ትወለዳለህ፤ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ 🔑 በጥርስ አልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ፤ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ። 🔐የሕይወትን ትግል እየዳህ ትጀምራለህ፤ አጎንብሰህ ትጨርሳለህ፡፡ 🌍ዘመንም ተምኔታዊ ነው፡፡ 🌅መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሃል፤ ሠኞ ማክሠኞ ብለህ ተጉዘህ፤ እንደገና ሠኞ ትላለህ፡፡ እናም ሕይወት አዙሪት ናት! 🌽መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው፤የጀመርክበትን አትርሳ፤ መጨረሻህ ነውና፡፡የጀመርክበትን አትናቀው፤ ትጨርስበታለህና፡፡ ተራ ሠው ሆነህ ትጀምራለህ፤ ተምረህ ዕውቀት ብትጨምርም፤ ነግደህ ሃብት ብታገኝ፤ ተሹመህ በሕዝብ ላይ ብትሠለጥን፤ ክቡረ ክቡራን ሆነህ የወርቅ ካባ ብትለብስ፤ የምትጨርሠው እንደተራ ሠው አፈር ለብሠህ ነው ተጨማሪ ያንብቡ
እቴጌ ጣይቱ ብጡል (ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ) - ፌብሩዋሪ 10, 2021 እቴጌ ጣይቱ ብጡል (ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ) «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ » በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ 12 ቀን 1832 ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ 80 ቀናቸው ጥቅምት 27 ቀን 1833 ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። በልጅነት ዘመናቸው በዚሁ ደብር ውስጥ ዳዊትን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በጊዜው ይሰጡ የነበሩትን ሌሎች የሃይማኖት ትምህርቶች በየታላላቁ አድባራት በመዘዋወር ያጠናቀቁ ስለመሆናቸው ታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ። የተማሩባቸውም መፃሕፍት ተጽፈው ይገኙ የነበረበትን የ ግዕዝ ቋንቋ አጣርተው ያውቁ ነበር። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። እቴጌ ጣይቱ (ያኔ ወ/ሮ) ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በጥበብና በህይወት ፍልስፍና የላቀ ችሎታ ባለቤት መሆናቸው እየታወቀ መጣ:: ፀሐፊ ትዕዛዝ ገ/ሥላሴ እንደፃፉት ይህንን የጣይቱን ዝና ከሰሙ ልዑላን መካከል አንዱ በጐንደር ከአፄ ቴዎድሮስ ጋር ይኖሩ የነበሩት ወጣቱ ምኒልክ ተጠቃሽ ናቸው:: አቤቶ ምኒልክ ስለ እቴጌ ጣይቱ ዝና የሰሙት አብረው ይኖሩ ከነበሩት አሉላና ወሌ ብጡ ተጨማሪ ያንብቡ
ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) - ፌብሩዋሪ 10, 2021 ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ ደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንጾር ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በጥቅምት 7 ቀን 1902ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት በቤተሰባቸው አጠገብና ባባታቸው አገር ደብረ- ኤልያስ ሄደው የግእዝ ትምሕርት ቤት ቅኔ ተቀኝተዋል። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ-ኤልያስ፣ በደብረ-ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ በ1918 ዓ.ም አዲስ አበባ በመሄድ በስዊድን ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ጊዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት ጣሊያን ወረራ ተከሰተ። የኢጣልያ ወረራ ሲከሰት ከልዑል ራስ ዕምሩ ኃይለሥላሴ ጦር ጋር በምዕራብ ኢትዮጵያ በአርበኝነት ሲዋጉ ቆይተው በመያዛቸው ጣሊያን ከልዑል ራስ ዕምሩ ጋር በግዞት ለሰባት ዓመታት በፖንዞ ደሴት ና በሊፓሪ ደሴት ታስረው ቆይተዋል። ከዚያም የተባባሪ ኃያላት ወታደሮች በ1935 ዓ.ም. ሲያስመልጧቸው በተመለሱበት ጊዜ በትምህርታቸው እንደገና በኦክስፎርድ ከገፉ በኋላ በተለያዩ የ መንግስት ተቋማት በተለይም በ ትምህርት ሚኒስቴር ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል። 1936 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኛ 1937 - 1938 - የኢትዮጵያ ቆንሱል በኢየሩሳሌም 1938 - በ International Telecommunications Conference አትላንቲክ ከተማ ፣ ኒው ጄርዚ ወኪል 1938- 1942 - በተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኒውዮርክ ሠራተኛ 1942- 1948 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይረክተርና ምክትል ተጨማሪ ያንብቡ
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ