Chemical Formula አገናኝ አግኝ ፌስቡክ X Pinterest ኢሜይል ሌሎች መተግበሪያዎች - ዲሴምበር 20, 2020 file:///storage/emulated/0/Chemical formula.pdfhttps://www.ambachewmu3.blogspot.com አገናኝ አግኝ ፌስቡክ X Pinterest ኢሜይል ሌሎች መተግበሪያዎች አስተያየቶች
ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) - ፌብሩዋሪ 10, 2021 ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ (ሃዲስ ኣለማየሁ) ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ ደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንጾር ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በጥቅምት 7 ቀን 1902ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት በቤተሰባቸው አጠገብና ባባታቸው አገር ደብረ- ኤልያስ ሄደው የግእዝ ትምሕርት ቤት ቅኔ ተቀኝተዋል። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ-ኤልያስ፣ በደብረ-ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ በ1918 ዓ.ም አዲስ አበባ በመሄድ በስዊድን ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ጊዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት ጣሊያን ወረራ ተከሰተ። የኢጣልያ ወረራ ሲከሰት ከልዑል ራስ ዕምሩ ኃይለሥላሴ ጦር ጋር በምዕራብ ኢትዮጵያ በአርበኝነት ሲዋጉ ቆይተው በመያዛቸው ጣሊያን ከልዑል ራስ ዕምሩ ጋር በግዞት ለሰባት ዓመታት በፖንዞ ደሴት ና በሊፓሪ ደሴት ታስረው ቆይተዋል። ከዚያም የተባባሪ ኃያላት ወታደሮች በ1935 ዓ.ም. ሲያስመልጧቸው በተመለሱበት ጊዜ በትምህርታቸው እንደገና በኦክስፎርድ ከገፉ በኋላ በተለያዩ የ መንግስት ተቋማት በተለይም በ ትምህርት ሚኒስቴር ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል። 1936 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኛ 1937 - 1938 - የኢትዮጵያ ቆንሱል በኢየሩሳሌም 1938 - በ International Telecommunications Conference አትላንቲክ ከተማ ፣ ኒው ጄርዚ ወኪል 1938- 1942 - በተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኒውዮርክ ሠራተኛ 1942- 1948 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይረክተርና ምክትል ... ተጨማሪ ያንብቡ
አማራ - ዲሴምበር 31, 2021 እኔ ሰው ብቻ ነኝ፣ እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ፣ እኔ ስልጡን ነኝ፣እኔ ምሁር ነኝ ፣ እኔ ሀይማኖተኛ ነኝ፣ እኔ ፖለቲካ አልወድም፣ እኔ በራሴ ፍልስፍና ነው የምመራው" የሚሉት ባህሪያት እንደአማራ አንድ ላይ ቆመን በአማራነቱ የገጠውን ፈተና አማራዊ መልስ ስጥቶ ነፃ እንዳይወጣ ያደረገው #በአባ_ባህርይ ዘመን የነበረው #የባህሪይ _ውርስ ነው ማነህ የእኛን ያህል የተገፋህ? እኛ ማለት እኮ... ➔አሀዳዊያን ተብለን የምንወዳትን አገር እንጠላ ዘንድ ማለቂያ የለሽ ግፍ የተፈጸመብን፤ ➔ "አማራ የለም" ተብሎ በሚዲያ ሲወራ የሰማን፤ ➔ዜግነትም ሆነ ማንነት የለሽ ሕዝብ መሆናችንን የሚገልጽ መጽሐፍ ተጽፎ ያነበብን፤ ➔"ሕዝብ ሳትሆኑ መንግሥት ናችሁ" በሚል የትግል ማኒፌስቶ ድምጽ የለሽ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የተፈጸመብን፤ ➔አማራን የሚያንቋሽሹና የሚያጠለሹ ሚዲያዎች ሪሲቨራችን ላይ የተጫነብን፤ ➔"አማራ ጠላት ሕዝብ ነው" ብለው የሚያምኑ ድርጅቶች ጥምረት ፈጥረው ጦርነት ያወጁብን፤ ➔ያልያዝነውን ሥልጣን እናስረክብ ዘንዳ "ዳውን ዳውን" የተባልን፤ ➔በእነ አቦይ ስብሐት አንደበት "እንዳያንሰራሩ አድርገን ሰብረናቸዋል" የሚል ጥናት የቀረበብን፤ ➔በቋንቋችን የተሳደድን፣ በማንነታችን የተጠቃን፣ በአገራዊ ፍቅራችን የተጣላን፤ ደስ የሚለው ነገር ታዲያ ይሄን ሁሉ በዴል የፈጸመብንና ጠላት ያደራጀብን አሸባሪ "አማራ ላይ የማወራርደው ሒሳብ አለኝ" በሚል እብሪት ወረራ ፈጽሞ ከእግራችን ስር መውደቁ ነው። በጎጃም፣ በጎንደር፣ በሸዋ ምድር የሚኖረው አማራም ወሎ መሬት ላይ ተሰባስቦ "አንቀጥቅጨዋለሁ" ባለው ተራራ ላይ እንደ ወባ እያንዘፈዘፈው ነው። ታዲያ ይሄን ታሪካዊ ክስ... ተጨማሪ ያንብቡ
እጅግ በጣም የሳትነው ብዙ ነገር አለ። - ኦክቶበር 15, 2021 እጅግ በጣም የሳትነው ብዙ ነገር አለ። እነዛ የሶሻሊዝምን ጽንሰ-ሃሳብ በውል ያልተረዱ፣ ጺማቸውንና ጠጉራቸውን የሚያሳድጉ የ60'ዎቹ ተማሪዎች "ማርክስ እንዳለው …፣ ኤንግልስ እንዳለው…፣ ሌኒን እንዳለው …፣ ማኦ እንዳለው …፣ ቼጉቬራ እንዳለው…፣ ሆቺሚኒ እንዳለው…፣ እስታሊን እንዳለው…፣ " ወዘተ እያሉ ታሪካችና እሴቶቻችን እንዲጠለሽ አድርገዋል። Twitter የ60'ዎቹ ትውልድ ባህሉን፣ ወጉን፣ ሥርዓቱን፣ ሥነ-ጽሑፉን፣ ታሪኩን ጭምር ነቅፎ በባዶ እጁ ነው የሸፈተው። ከቆዳ ቀለማቸው በስተቀር የኢትዮጵያዊነትን ነባር እሴት፣ ባህል፣ ወግ፣ ታሪክ... ፍቀው የነማርክስንና የነስታሊን ፍልስፍና ይዘው ነው የሸፈቱት። መፍትሔው እግዚአብሔርን መካድ የመሰለው ማርክሲዝምን ርዕዮተ ዓለም አድርጎ የተነሣው የሶሻሊስት አቀንቃኝና የብሔር ፖለቲካን ቀይጦ የያዘው ወጣት የኢትዮጵያዊነት አስኳል ከውስጣቸው አውጥተው ጣሉት። በአጉል ማርክሳዊ-ሌኒናዊነት እግዚአብሔር-አልባ አደረጋቸው። ትውልዱንም ሳይቀራረብ የሚተያይ፣ በማያውቀው ታሪክ ተተብትቦ ወደኋላ እንጂ ወደፊት መራመድ የማይችል፣ ባዕድን እንደ ዘመድ፤ ዘመድን እንደ ባዕድ የሚመለከት ሽባ ትውልድ አደረጉት። እንጥፍጣፊ ሳያስቀር የኩራቱንና የክብሩን ካባ አውልቆ ጣለው፣ ኢትዮጵያዊነትን በአፍጢሙ ደፋው፣ የመንፈስ ኃይሉ ደቀቀ፣ በመጨረሻም አንገቱን ደፋ፣ ችግሩንም ሁሉ ለመፍታት የፈረንጆችን እርዳታ የሚፈልግ ትውልድ ተፈጠረ። ቀጥሎስ.....ቀጥሎ ደግሞ የኢትዮጵያ እደ ጥበብ ሠራተኞችን፦ ለምሳሌ ብረት ሰሪዎችን "ቀጥቃጭ"፣ ልብስ ሰሪዎችን "ሸማኔ"፣ ቆዳ ሰሪዎችን "ፋቂ" በማለት እንዲጠፉና ከማኅበረሰቡ እንዲገለሉ አደረገ። ይህ ቅስቀሳ በሚሲዮናውያን የተ... ተጨማሪ ያንብቡ
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ